ሄሮድያዳ መጥምቁ ዮሐንስ ባገለገለበት ዘመን ይሁዳን እየገዛ የነበረው ንጉሥ ሄሮድስ (አንቲጳስ) ሚስት ነበረች።
ሄኖክ የሁለት የብሉይ ኪዳን ሰዎች ስም ነው።
ሆሴዕ ከክርስቶስ 750 ዓመት በፊት የእስራኤል ነቢይ ነበር።
ሆሺያ (ሆሴዕ) በይሁዳ ነገሥታት በአካዝና በሕዝቅያስ ግዛት ዘመን ለዘጠኝ ዓመት የእስራኤል ንጉሥ ነበር።
ሉቃስ አዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉ ሁለት መጻሕፍት የሉቃስ ወንጌልና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ነው።
ሊባኖስ ከእስራኤል በስተ ሰሜን ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ በጣም የምታምር ተራራማ ቦታ ናት። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ይህ አካባቢ ጥቅጥቅ ባሉት ደኖቹም ይታወቅ ነበር።
ላሜሕ ዘፍጥረት ውስጥ የተጠቀሱ የሁለት ሰዎች ስም ነው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ላባን የያዕቆብ አጎትና አማት ነበር።
“ሌዋታን” የሚለው ቃል በቀደሙት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የተጠቀሰ በጣም ግዙፍና አሁን የማይገኝ አውሬ ነው።
ሌዋዊ የሌዊ ዘር የሆነ የእስራኤል ማኅበረ ሰብ አባል ነው።
ልስጥራ በአንዱ ሐዋርያዊ ጕዞው ጳውሎስ የጎበኛት ታናሽ እስያ ውስጥ የነበረች ከተማ ስም ነው። የምትገኘው የአሁንዋ ቱርክ ባለችበት ሊቃኦንያ አካባቢ ነበር።
ልያ ከያዕቆብ ሚስቶች አንኳ ነበረች። የዐሥር ወንዶች ልጆች እናት ስትሆን ዐሥሩ ልጆች ከእስራኤል ነገዶች የተወሰኑት ነበሩ።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሎጥ የአብርሃም ወንድም ልጅ ነበር።
ሐማት ከምድረ ከነዓን በስተ ሰሜናዊ ሶርያ ውስጥ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ናት። በዚህ ዘመን የከተማዋ ስም ሐማ ይባላል።
ሐራን የአብርሃም ታናሽ ወንድምና የሎጥ አባት ነበር።
ሐና ከ6-15 ዓ፤ም ከ10 ዓመት በእየሩሳሌም የነበረ አይሁዳዊ ሊቀ ካህን ነው፤ይሁን እንጂ በኋላ ላይ ሮማውያን ከሊቀ ካህንነቱ አንስተውታል፤ያም ሆኖ በአይሁድ ዘንድ የነበርው ተደማጭነት መሪ በመሆን ቀጥሎ ነበር።
ሐና ብሉይ ኪዳኑ ውስጥ የነቢዩ ሳሙኤል እናት ናት። ከሕልቃና ሚስቶች አንዷ ነበረች።
ሐጌ እስራኤል ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ በኋላ የነበረ የይሁዳ ነቢይ ነበር።
ይህ የመጀመሪያዋ ሴት ስም ነበር። የስሟ ትርጉም፣ “ሕይወት” ወይም፣ “ሕያው” ማለት ነው።
ሕዝቅኤል ብዙ አይሁድ ወደባቢሎን በተወሰዱበት የምርኮ ወቅት የነበረ የእግዚአብሔር ነብይ ነው።
ሕዝቅያስ 13ኛው የይሁዳ ንጉሥ ነበር። በእግዚአብሔር የሚታመንና ለእርሱ የሚታዘዝ ንጉሥ ነበር።
አብርሃም በነበረበት ዘመን መልከጼዴቅ፣ በኋላ፣ “ኢየሩሳሌም” ተብላ የተጠራችው የሳሌም ከተማ ንጉሥ ነበር።
መርዶክዮስ በፋርስ አገር ይኖር የነበረ አንድ አይሁዳዊ ስም ነው። በኋላ ላይ የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ሚስት የሆነችው የአጎቱ ልጅ የአስቴር ጠባቂ ነበር።
መስጴጦምያ በኤፍራጥስና በጤግሮስ ወንዞች መካከል ያለ ምድር ነው። ስፍራው የዘመኑ ኢራቅ ያለችበት ቦታ ነበር።
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን መቄዶንያ ከጥንቱ ግሪክ በስተ ሰሜን የነበረች የሮም አውራጃ ነበረች።
መዓካ የአብርሃም ወንድም ናሆር ከወለዳቸው ልጆች አንደኘው ነው። በብሉይ ኪዳን ሌሎችም ሰዎች ይህ ስም ነበራቸው።
ሙሴ ለ40 ዓመት የእስራኤል ሕዝብ ነቢይና መሪ ነበር።
ሚልክያስ ወደ እስራኤል ከተላኩት የእግዚአብሔር ነቢያት አንዱ ነው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሚሳኤል ተብለው የተጠሩ ሦስት ሰዎች አሉ።
ሚካኤል ቅዱሳንና ታዛዦች ከሆኑት የእግዚአብሔር መላእክት ዋናው ነው። የእግዚአብሔር፣ “ሊቀ መልአክ” ተብሎ የተጠራ እርሱ ብቻ ነው።
ሚክያስ ነቢዩ ኢሳይያስም በይሁዳ እያገለገለ በነበረ ጊዜ ከክርስቶስ 700 ዓመት በፊት የነበረ የይሁዳ ነቢይ ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሚጽጳ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ቦታዎች አሉ። ትርጕሙ፣ “መመልከቻ ቦታ” ወይም፣ “ቅጥር መጠበቂያ” ማለት ነው።
ማርታ ቢታንያ በተባለ ቦታ ትኖር የነበረ የኢየሱስ ተከታይ ሴት ናት።
ማርያም የአሮንና የሙሴ ታላቅ እኅት ነበረች።
ማርያም ቢታንያ በሚባል ቦታ ትኖር የነበረ የኢየሱስ ተከታይ ናት።
ማርያም መግደላዊት ኢየሱስን መከተል የጀመረችው ሰባት አጋንንት ከእርሷ ካስወጣ በኋላ ነበር።
ማርያም የዮሴፍ እጮኛና የኢየሱስ እናት ናት።
ማቴዎስ ለእልፍዮስ ልጅ ለሌዊ የተሰጠ ስም ነው። ማቴዎስ ሐዋርያቱ እንዲሆኑ ኢየሱስ ከመረጣቸው አሥራ ሁለት ሰዎች አንዱ ነበር።
ሜምፊስ ዐባይ ወንዝ መደዳ የምትገኝ ጥንታዊ ግብፅ ውስጥ የነበረች ከተማ ነበረች።
ሜዶን ከአሦርና ከባቢሎን በስተ ምሥራቅ፣ ከኤላምና ከፋርስ በስተ ሰሜን የነበረ ትንታዊ መንግሥት ነው። የነበረበት ቦታ በአሁኑ ዘመን ቱርክ፣ ኢራን፣ ሶርያ፣ ኢራቅና አፍጋኒስታን ያሉበትን በክፊል ያካትት ነበር።
ምሳሕ የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ነው። ሌላው ሞሳሕ ተብሎ የተጠራ ሰው የኖኅ ልጅ የሴም የልጅ ልጅ ነው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ምናሴ ተብለው የተጠሩ አምስት ሰዎች ነበር።
ምድያማውያን ከከነዓን በስተ ደቡብ ሰሜናዊው የአረቢያ ምድረ በዳ ይገኙ የነበሩ ሕዝብ ናቸው።
ሞሎም ከነዓናውያን ከሚያመልኳቸው ሐሰተኛ አማልክት የአንዱ ስም ነበር።
ሞዓብ የኖኅ ታላቅ ሴት ልጅ ልጅ ነበር። ዘሮቹ ሞዓባውያን ሲባሉ የሰፈሩበት ቦታ ሞዓብ ተባለ።
አጠቃላይ በሆነ አነጋገር፣ “ሠሪ” ነገሮችን የሚፈጥር ወይም የሚሠራ ማለት ነው።
ረባት በጣም ጠቃሚ የአሞራውያን ከተማ ነበረች።
ረዓብ እስራኤላውያን ኢያሪኮን ሲያጠቁ እዚያ የነበረች ሴት ነበረች። አመንዝራም ነበረች።
ሩት መሳፍንት እስራኤላውያንን እየመሩ በነበረ ዘመን የነበረች ሞዓባዊት ሴት ናት። ጥንታዊ የኢየሱስ ክርስቶስ መገኛ ነበረች
ሪሞን የአንድ ሰው እና መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሳቸው ጥቂት ቦታዎች ስም ነው። ሪሞን የሚባል ጣዖትም ነበር። ቃል በቃል ትርጉሙ፣ “ሮማን” ማለት ነው።
ራሔል ከያዕቆብ ሚስቶች አንዷ ነበረች። እርሷና እኅቷ ልያ የያዕቆብ አጎት የላባን ልጆች ነበሩ።
ራማ ከኢየሩሳሌም በስተ ሰሜን 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ጥንታዊ የእስራኤል ከተማ ነበረች።
ራሞት ገለዓድ ተራሮች ላይ የምትገኝ በጣም ጠቃሚ ከተማ ነበረች። ራሞት ገለዓድም ትባላለች።
ርብቃ ከአብርሃም ወንድም ልጆች አንዷ ነበረች፤ የእርሷ አያት የአብርሃም ወንድም ነበር።
በዚህ ባለንበት ዘመን ሮም የኢጣልያ ዋና ከተማ ናት።
ሮቤል የመጀመሪያው የያዕቆብ ልጅ ነበር። እናቱ ልያ ትባላለች።
ሮብዓም ከንጉሥ ሰሎሞን ልጆች አንዱ ሲሆን፣ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤል ሕዝብ ንጉሥ ሆኗል.
ሰሎሞን ከንጉሥ ዳዊት ልጆች አንዱ ነበር። የእናቱ ስም ቤርሳቤህ ይባል ነበር
ሰማርያ ለእስራኤል ሰሜናዊ አካባቢ ላለው ከተማና አካባቢው የተሰጠ ስም ነው። ይህ አካባቢ በምዕራብ በሳሮን ሜዳማ ቦታና በምሥራቅ በኩል በዮርዳኖስ ወንዝ መካከል ይገኛል
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሰሜኢ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ሰዎች ነበሩ።
ሰናክሬም ነነዌ ሀብታምና ተፈላጊ ከተማ እንድትሆን ታላቅ የአሦር ንጉሥ ነበር
ሰናዖር፣ “የሁለት ወንዞች አገር” ማለት ሲሆን በደቡባዊ ሜሶፖታሚያ ላለው ሜዳ ወይም አካባቢ የተሰጠ ስም ነበር
ሰዶም የአብርሃም ወንድም ልጅ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር ይኖርበት የነበረ ከከነዓን በስተ ደቡብ አካባቢ ያለ ከተማ ነበር
ካህንና ነቢይን ጨምሮ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሶፎንያስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ሰዎች ነበር። የሶፎንያስ ትንቢት የሚገኘው ትንቢተ ሶፎንያስ ውስጥነው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሱኮት ተብለው የተጠሩ ሁለት ከተሞች አሉ። ሱኮት “መጠለያ” ወይም፣ “መጠጊያ” ማለት ነው
ሲላስ በኢየሩሳሌም በነበሩ አማኞች መካከል መሪ ነበር
ሲና በአሁኑ ዘመን የሲና ፔኔንሱላ ተብሎ በሚጠራው ደቡባዊ ክፍል የሚገኝ ተራራ ስም ነው
ሲዶን የከነዓን የመጀመሪያ ልጅ ነበር፤ ሲዶን የምትባል የከነዓናውያን ከተማም አለች
ሳሙኤል የመጨረሻው የእስራኤል መስፍን እና ነቢይ ነበር፤ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆኑ ሳኦልንና ዳዊትን የቀባው እርሱ ነበር
ሳምሶን ከእስራኤል መሳፍንት ወይም ታዳጊ አንዱ ነበር። ሳምሶን ከዳን ነገድ ነበር።
ሳሮን ከቀርሜሎስ ተራራ በስተ ደቡብ ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ጠፍጣፋና ለም ምድር ነው። “የሳሮን ሜዳ” በመባልም ይታወቃል
በጥንት ዘመን ሳባ ደቡብ አረቢያ አንድ ቦታ የሚገኝ ሥልጣኔ ወይም አካባቢ ነበር
ሳኦል የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን እግዚአብሔር የመረጠው እስራኤላዊ ነበር
ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ ሳኦል የሚሉት ሌላ እስራኤላዊ ነበር፤ በኢየሱስ ካመነ በኋላ እግዚአብሔር ስሙን ጳውሎስ ወደሚል ለወጠው
ሳዶቅ በንጉሥ ዳዊት ዘመን በእስራኤል የነበረ ሁነኛ ሊቀ ካህን ነበር።
ሴሎ በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን አሸንፈው የያዟት በግንብ የተከበበች የከነዓናውያን ከተማ ነበረች
ሴም ከሦስቱ የኖኅ ወንዶች ልጆች አንዱ ሲሆን፣ ኦሪት ዘፍጥረት ውስጥ የተለጸው የጥፋት ውሃ በመጣ ጊዜ ከአባቱ ጋር መርከቡ ውስጥ ገብቶ ነበር
ሴት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሰ ሦስተኛው የአዳምና የሔዋን ልጅ ነበር
ሴኬም ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን 40 ማይል ርቀት ላይ የሚገኝ ከነዓን ውስጥ የነበረ ከተማ ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሴኬም ተብሎ የተጠራ ሰው ነበር።
ሴዴቅያስ የመጨረሻው የይሁዳ ንጉሥ ነው (597-587 ዓቅክ)።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስምዖን የተባሉ ጥቂት ሰዎች ነበሩ
ሶርያ ከእስራኤል ሰሜን ምሥራቅ የሚገኝ አገር ነው። አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን በሮም መንግሥት የሚተዳደር አገር ነው
ቀሬና ከአፍሪካ ሰሜናዊ ባሕር ዳርቻ ሜዲትራንያን ባሕር ላይ ከቀርጤስ ደሴት ደቡብ ትገኝ የነበረች የግሪክ ከተማ ናት።
“የቀርሜሎስ ተራራ” በሜዲትራንያን ባሕር አካባቢ ከሳሮን ሜዳማ ቦታ በስተ ሰሜን የነበረውን የተራራ ተረተር ያመለክታል። በጣም ትልቁ ጫፍ 546 ሜትር ከፍታ አለው።
ቀርጤስ ግሪክ ደቡባዊ ባሕር ዳርቻ ማዶ ትገኝ የነበረች ደሴት ናት። የቀርጤስ ሰው በቀርጤስ የሚኖር ሰው ነው።
ቀናተኛው ስምዖን ከአሥራ ሁለት የኢየሱስ የቅርብ ደቀመዛሙርት አንዱ ነበር
ቀያፋ መጥምቁ ዮሐንስና ኢየሱስ ባገለገሉበት ዘመን የእስራኤል ሊቀ ካህን ነበር።
ቂቶስ በወታደራው ድል በ550 ዓ.ቅ.ክ. ገደማ የፋርስ መንግሥትን የመሠረተ ነበር። በዓለም ትሪክ ታላቁ ቂሮስ በመባልም ይታወቃል።
ቃና ናዝሬት በስተ ሰሜን ዘጠኝ ማይሎች ያህል ርቃ የምትገኝ ገሊላ አውራጃ ውስጥ ያለች መንደር ወይም ከተማ ነበረች።
ቃየንና ታናሽ ወንድሙ አቤል መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ የመጀመሪያ የአዳምና የሔዋን ልጆች ናቸው።
ቃዴስ ወይም ቀዴስ በርኔ በአሁኑ ጊዜ ሶርያ በሚባለው ውስጥ የምትገኝ በእስራኤል ታሪክ ውስጥ ጠቃሚ የሆነች ከተማ ነበረች።
ቃዴስ ወደ ምድር ከነዓን በገቡ ጊዜ እስራኤላውያን የወሰዷት ከነዓናዊ ከተማ ነበረች።
“ቄሳር” የተሰኘው ቃል ብዙዎቹ የሮም ገዦች የሚጠቀሙበት ስም ወይም መጠሪያ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ መጠሪያ ሦስት ገዦችን ያመለክታል።
ቂሳርያ ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ፣ ከቀርሜሎስ ተራራ 39 ኪ.ሜ. ርቃ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ነበረች። ፊልጶስ ቂሳርያ ከእስራኤል ሰሜን ምሥራቃዊ ክፍል አርሞንዔም ተራራ አጠገብ ያለች ከተማ ነበረች።
ቄዳር የእስማኤል ሁለተኛ ልጅ ሲሆን፣ ከእርሱ ዘሮች ብዙ ሕዝብ ያለው ነበር። ቄዳር የምትባል ታውቂ ከተማም አለች።
ቅፍርናሆም ከገሊላ ባሕር ዳርቻ ሰሜን ምዕራብ የምትገኝ ዓሣ የሚጠመድባት ቦታ ናት።
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ቆላስይስ ፍርግያ በምትባለው የሮማውያን ግዛት ውስጥ የነበረች ከተማ ስትሆን በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው ከቱርክ ደቡብ ምዕራብ ባለው አካባቢ ነው። የቆላስይስ ሰዎች ቆላስይስ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ናቸው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ቆሬ በትንሹ የሁለት ሰዎች ስም ነው።
ቆርኔሌዎስ በትውልድ አይሁድ ያልሆነ የሮም ወታደሮች ባለ ሥልጣን ነበር።
ቆሮንቶስ ከአቴና በስተ ምዕራብ 50 ማይል ርቃ የምትገኝ የግሪክ ከተማ ነበረች። የቆሮንቶስ ሰዎች በቆሮንቶስ የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው።
ቆጵሮስ ከዘመኑ ቱርክ በስተ ደቡብ 64 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች ሜዲትራንያን ባሕር ላይ ያለች ደሴት ናት።
በለዓም ወደ ከነዓን ምድር ለመግባት በሰሜናዊ ሞዓብ ሰፍረው በነበረ ጊዜ እስራኤልን እንዲረግም ንጉሥ ባላቅ ቀጥሮት የነበር አረማዊ ነብይ ነበር።
በርባን ኢየሱስ በተያዘ ጊዜ ኢየሩሳሌም ውስጥ የነበር እስረኛ ነበር
በርተሎሜዎስ ከአስራ ሁለት የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር
በርናባስ በሐዋርያት ዘመን የነበረ ከጥንት ክርስቲያኖች አንዱ ነበር
ብሉይ ኪዳን ውስጥ መናያስ በሚል ስም የሚታወቁ ጥቂት ሰዎች ነበሩ
“በኣል” ፦ “ጌታ” ወይም፥ “አለቃ” ማለት ሲሆን፥ ከነዓናውያን ከሚያመልኳቸው ዋነኞቹ ጣዖቶች የአንዱ ስም ነበር።
ቢታንያ ከኢየሩሳሌም ምሥራቅ 2ማይል ርቀት ላይ ከደብረ ዘይት ተራራ ምሥራቅ ባለው ተዳፋት ግርጌ የምትገኝ ከተማ ነበረች
መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ታላቁ ባሕር” ወይም፣ “የምዕራብ ባሕር” የሚለው በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የነበሩ ሰዎች ከሚያውቁት ባሕር ትልቁ የነበረው፣ ሜዲትራንያን ባሕርን ነው።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ባሮክ በመባል የሚታወቁ የተለያዩ ሰዎች አሉ
ባሳን ከገሊላ ባሕር በስተምስራቅ አካባቢ ያለ ቦታ ነው። በአሁኑ ዘመን የሶርያ አካል የሆነውን አካባቢና የጎላን ኮረብታን ይሸፍናል
የባቢሎን ከተማ የጥንት ባቢሎንያ አካባቢ ዋና ከተማ ሲሆን፥ የባቢሎን መንግሥት ግዛት አካልም ነበር
ባቤል ከመሰጵጦምያ በስተደቡብ በነበረችው ሰናዖር በምትባል አካባቢ ዋነኛ ከተማ ነበረች በኋላ ላይ ሰናዖር ባቢሎን ተብላለች
ባቱኤል የአብርሃም ወንድም የናኮር ልጅ ነበር
ባኦስ እስራኤል ሐሰተኛ አማልክትን እንዲያመልኩ ካደረጉ የእስራኤል ነገሥታት አንዱ ነበር
ቤርሳቤህ በዳዊት ሰራዊት ውስጥ ወታደር የነበርው የኦርዮን ሚስት ነበረች። ኦርዮን ከተገደለ በኋላ የዳዊት ሚስትና የሰሎሞን እናት ሆናለች
ብሉይ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ቤርሳቤህ አሁን ኔጌቭ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው በረሐ ውስጥ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምዕራብ 45 ማይሎች ላይ የምትገኝ ከተማ ነበረች
አዲስ ኪዳን ውስጥ ቤርያ ከመቄዶንያ ደቡብ ምስራቅ ከተሰሎንቄ በስተደቡብ 80 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ በጣም ሀብታም የግሪክ ከተማ ነበርች።
ቤተልሔም ኢየሩሳሌም ከተማ አጠገብ የምትገኝ አንዲት ትንሽ የእስራኤል ከተማ ነበረች። “ኤፍራታ” በመባልም ትታወቃለች፤ ምናልባት የመጀመሪያ ስሟ ይህ ሳይሆን አይቀርም
ቤቴል ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን ከነዓን ምድር ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነበረች። የቀድሞ ስሟ “ሎዛ” ነበር
ቤትሳሚስ ከኢየሩሳሌም በስተምዕራብ በግምት 30ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ከነዓናዊት ከተማ ስም ነው
ብንያም ከያዕቆብና ከሚስቱ ከራሔል የተወለደ የመጨረሻው ልጅ ነው። የስሙ ትርጉም ፥ “የቀኝ እጄ ልጅ” ማለት ነው።
ብዔልዜቡል የአጋንንት አለቃ ሲሆን፥ የሰይጣን ወይም የድያብሎስ ሌላ ስም ነው
በዔዝ የሩት ባል፣ የንጉሥ ዳዊት አያትና ኢየሱስ የተገኘበት ዘር ዋና ግንድ የነበረ እስራኤላዊ ነበር።
ተርሴስ የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ልጅ ስም ነው
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ተሰሎንቄ በጥንቱ የሮም ግዛት ውስጥ የነበረችው የመቄዶንያ ዋና ከተማ ነበረች። በዚያ ከተማ የነበሩ፣ “የተሰሎንቄ ሰዎች” ይባላሉ።
ቲርዛ በጣም ጠቃሚ የከነዓናውያን ከተማ ነበረች፤ በኋላም የሰሜናዊው የእስራእል መንግሥት ጊዜያዊ ዋና ከተሞች አንዷ ሆና ነበር።
ቲቶ ሐዋርያው ጳውሎስ ያስተማረው የጥንት ቤተ ክርስቲያን መሪ ነበር።
ቲኪቆስ ከጳውሎስ ጋር የወንጌል አገልጋዮች ከነበሩት አንዱ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሄሮድስ የሚባሉ ጥቂት ገዦች ነበር። ኢየሱስ በተወለደ ዘመን ሄሮድስ አይሁድ ያልሆነ የይሁዳ ንጉሥ ነበር።
ታራ የኖኅ ልጅ የሴም ዘር ነው። የአብርሃም፣ የናኮርና የካራን አባት ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ትዕማር ተብለው የተጠሩ በርካታ ሴቶች ነበሩ። ትንቢተ ሕዝቅኤል ውስጥ ትዕማር የተባለ ቦታ ተጠቅሷል
ቶማስ ደቀ መዛሙርቱ እንዲሆኑ ኢየሱስ ከመረጣቸው ሰዎች አንዱ ነበር (ሐዋርያት ተብለዋል)።
ቶቤል የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ነው።
ነህምያ የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ በባቢሎናውያን በምርኮኝነት በተወሰዱ ጊዜ ባቢሎን መንግሥት ውስጥ ይኖር የነበረ እስራኤላዊ ነው።
ነነዌ የአሦር ዋና ከተማ ነበረች። የነነዌ ሰዎች ነነዌ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ናቸው።
ናሆም ክፉው ንጉሥ ምናሴ እየገዛ በነበረበት ዘመን ያገለገለ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበር።
ናቡከደነፆር የባቢሎን መንግሥት ንጉሥ ነበር። የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት በነበሩበት ዘመን ባቢሎን ገናና መንግጥ ነበረች።
ናትን ዳዊት የእስራኤል ንጉሥ በሆነበት ዘመን የኖረ ታማኝ የእግዚአብሔር ነቢይ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ናኮር ተብለው ከተጠሩ ሁለት ሰዎች አንደኛው የአብርሃም አያት ሲሆን፣ ሁለተኛው የአብርሃም ወንድም ነበር።
ናዝሬት በሰሜናዊ እስራኤል ገሊላ አውራጃ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነች።
ኔጌብ በደቡባዊ እስራኤል የሚገኝ በረሃማ አካባቢ ነው።
ንዕማን የእስራኤል ጠላቶች አንዱ የነበረው የሶርያ ጦር አዛዥ ነበር።
ንፍታሌም ስድስተኛው የያዕቆብ ልጅ ነው። የእርሱ ዘሮች ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ የሆነውን የንፍታሌም ነገድ አስገኝተዋል።
ኖኅ በዓለም የነበሩ ክፉ ሰዎችን ለማጥፋት እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ የሚያዳርስ ጎርፍ በላከበት ጊዜ ከ4000 ዓመት በፊት ይኖር የነበረ ሰው ነው። ጎርፉ ምድርን በሚሸፍንበት ጊዜ እርሱና ቤተ ሰቡ የሚኖሩበት ግዙፍ መርከብ እንዲሠራ እግዚአብሔር ለኖኅ ነገረው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልዓዛር የበርካታ ስሞች ስም ነበር።
አልዓዛር ኢየሱስ ከሞት ያስነሣው ወዳጁ ነበር።
አማሌቃዊ ከኔጌብ ምድረ በዳ አንሥቶ እስከ አረብ አገር ድረስ ባለው የከነዓን ደቡባዊ ክፍል በሙሉ የሚኖሩ ዘላን ሕዝብ ነበሩ።እነዚህ ሰዎች የኤሳው ልጅ ልጅ የአማሌቅ ዘሮች ናቸው።
አባቱ ንጉሥ አዩአስ ከተገደለ በኋላ አሜስያስ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ።
ከአኪናሆም የተወለደ የዳዊት ታላቅ ልጅ ነው፤፤
አሞራውያን ከኖህ የልጅ ልጅ ከከነዕን የተገኘ ሃያል ህዝብ ነበሩ፤
“የአሞን ሕዝብ” ወይም ፣ “አሞናውያን” ከነዓን ውስጥ ከነበሩት ሕዝቦች አንዱ ናቸው።ሎጥ ከትናሿ ልጁ የወለደው የቤን አሚ ዘር ናቸው።
አሞጽ በይሁዳ ንጉስ በዕዝያን ዘመን የነበረ እስራኤላዊ ነብይ ነበር፤
የነቢዩ ኢሳይያስ አባት አሞጽ ይባል ነበር።
አሦር እስራኤል በከነዓን ምድር ይኖሩ በነበሩበት ዘመን በጣም ኅያል መንግሥት ነበር። የአሦር መንግሥት በአሦር ንጉሥ ይተዳደሩ የነበሩ አገሮች ናቸው።
አረቢያ፥3000000 ስኩዬር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የዓለማችን ትልቁ ባሕር ገቡ፤አካባቢ ነው ከእስኤል ደቡብ ምስራቅ ያለ ቦታ ሲሆን ከቀይ ባሕር ከአረቢያ ባሕርና ከፋርስ ባሕር ሰላጤ ጋር ይዋስናል።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ አርም የሁለት ሰዎች ስም ነው፤የአሁኑ ሲሪያ ያለችበት ከከነዓን ሰሜን ምስራቅ ያለው አካባቢ ስም ነው፤
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “አራራት” ለአንድ አካባቢ፥ ለአንድ መንግሥትና የተራራ ሰንሰለት የተሰጠ ስም ነው።
አርሞንዔም ተራራ እስራኤል ውስጥ ካሉ ተራሮች በጣም ረጁም ነው።
አርጤክስስ ሃያ ዓመት የጥንቱን ፋርስ/ኢራቅ የገዛ ንጉሥ ነበር።
አርጤክስስ ከ 464-424 ዓቅክ የፋርስን መንግሥት ሲገዛ የነበረ ንጉሥ ነው
አሮን የሙሴ ታላቅ ወንድም ነበር። የእስራኤል ሕዝብ የመጀመሪያ ሊቀ ካህን እንዲሆን እግዚአብሔር አሮንን መረጠ።
አሳ ክ913-873 አቅክ ድረስ ለአርባ ዓመት የይሁዳን መንግሥት የገዛ ንጉሥ ነበር
አሳፍ ሌዋዊ ካህን ሲሆን፥ ለንጉሥ ዳዊት መዝሙሮች ሙዚቃ ያዘጋጀ ጥሩ ስጦታ ያለው ሙዚቀኛ ነበር። አሳፍ የራሱን መዝሙሮችም ጽፎአል
አሴር የያዕቆብ ስምንተኛ ልጅ ነው። የእርሱ ዘሮች ከአሥራ ሁሉቱ የእስራኤል ነገድ አንዱ ሆኑ፤ ዘሮቹም “አሴር” ተብለው ይጠራሉ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን አስቀሎና ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ ዋና የፍልስጥኤማውያን ከተማ ነበርች። ዛሬም እስራኤል ውስጥ ትገኛለች።
የአስቆሮቱ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ለአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠ እርሱ ነበር።
አይሁድ በባቢሎን በምርኮ በነበሩበት ዘመን የፋርስ መንግሥት ልዕልት የሆነች አይሁዳዊት ሴት ናት።
ከመጽሐፈ አስቴር እንደምንመለከተው አስጢን የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ሚስት ነበረች።
አሼራ በብሉይ ኪዳን ዘመን ከነዓናውያን ያመልኳት የነበሩ ጣዖት ነበረች። “አስታሮት” ሌላው የአሼራ ስም ነው፥ ወይም ደግሞ ተመሳሳይ የሆነች ሌላ ጣዖት ስም ሊሆን ይችላል።
አሽዶድ ከአምስቱ በጣም ጠቃሚ የፍልስጥኤም ከተሞች አንዷ ነበረች። ሜድትራኒያን ባሕር አጠገብ ከከነዓን ደቡብ ምዕራብ፥ በጋዛና በኢዮጴ መካከል ግማሽ ርቀት ላይ ነበር የምትገኘው
አቂላ ከጥኩር በቀር ደቡባዊ ባሕር ዳርቻ ከነበረው ጻንጦስ አውራጃ የነበረ አየሁዳዊ ነበር፤
አቃሮን የፍልስጥኤማውያን ዋነኛ ከተማ ሲሆን የሚገኘው ከሜድትራንያን ባሕር ዘጠኝ ማይል ገባ ብሎ ያለ ቦታ ላይ ነበር።
አብርሃምና ይስሐቅ በከነዓን ምድር በሚኖሩበት ዘመን አቢሜሌክ በጌራራ አካባቢ የነገሠ ንጉስ ነበር ።
ከ 915- 913 ዓቅክ ነግሦ የነበር የይሁዳ ንጉሥ ስም ነው እርሱ የንጉሥ ሮብዓም ልጅ ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ አቢያ የሚል ስም የሚታወቁ ሌሎች ጥቂት ሰዎችም ነበሩ።
አቤል የአዳምና የሔዋን ሁለተኛ ልጅ ነበር። እርሱ የቃየል ታናሽ ወንድም ነበር።
አቤሴሎም የዳዊት ሦስተኛ ወንድ ልጅ ነበር። በቁንጅናውና በቁመናው እንዲሁም በጣም ቅብጥብጥ በመሆኑ ይታወቃል።
አቤኔር የንጉሥ ሳኦል አጎት ልጅ ነበር።
አብራም የእስራኤላውያን አባት እንዲሆን እግዚአብሔር የመረጠው ከዑር ከተማ የመጣ ከለዳዊ ነበር። በኋላ ላይ እግዚአብሔር “አብርሃም” በማለት ስሙን ለውጦታል።
በንጉሥ ዳዊት ዘመን አብያታር የእስራኤል ሕዝብ ሊቀ ካህን ነበር።
አብድዩ በንጉሥ ሕዝቅያስ ዘመን ከነበሩ የእስራኤል ነቢያት አንዱ ነበር።
ከትንቢተ ዳንኤል እንደምንመለከተው አናንያ በምርኮ ዘመን ወደ ባቢሎን ተወስደው ስለነበሩ አስተዋይ አይሁዳውያን ወጣቶች አንዱ ነበር። ይበልጥ የሚታወቀው ሲድራቅ በተሰኘው ስሙ ነው።
አዲስ ኪዳን ውስጥ አንጾኪያ የሁለት ከተሞች ስም ነበር፤አንደኛው ሜድትርያን ባሕር ዳርቻ አጠገብ በሶሪያ ነበር፤ሌላው ግን ቆላስያስ ከተማ አጠገበ በነረው ጺስዲያ ነበር።
አኪያ ብሉይ ኪዳን ውስጥ የተለያዩ ሰዎች ስም ነው። የሚከተሉት ከእነዚህ ሰዎች ጥቂቶቹ ናቸው፣
አካዝ ከ732 ዓቅከ - 716 ዓክከ የይሁዳን መንግሥት የገዛ በጣም ክፉ ንጉሥ ነበር። ይህ ይሆነው በእስራኤልና በይሁዳ የነበሩ ብዙ ሰዎች በምርኮ ወደ ባቢሎን ከመወሰዳቸው 140 ዓመት በፊት ነበር።
አካዝያስ የሁለት ንጉሦች ስም ነው፤አንደኛው የእስራኤል መንግሥት ስገዛ ሌላው የይሁዳን መንግሥት ገዛ።
አክዓብ ከ 875-854 ዓቅክ ስሜናዊ የእስራኤል መንግሥት ላይ ነግሦ የነበረ በጣም ክፉ ንጉሥ ነው።
በብሉይ ኪዳን ውስጥ አዛርያስ በሚባል ስም የታወቁ ሰዎች ነበሩ
አዳም እግዚአብሔር የፈጠረው የመጀመሪያ ሰው ነው።እርሱና ሚስቱ ሔዋን በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ተፈጥረዋል።
አዶንያስ የንጉሥ ዳዎት አራተኛ ልጅ ነው።
አጋር የሦራ አገልጋይ ነበረች።
አጽሎስ ግሪክ ዉስጥ ከነበረው እስክንድሪያ የመጣ ስለ እየሱስ ለሰወች ለማስተማር ልዩ ችሎታ የነበረው አይሁዳዊ ነበር።
አፍራታ በሰሜኑ የእሥራኤል ክፍል የሚገኝ የአንድ ከተማ ስም ነበር።
ኢሳይያስ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበር።
ኤቄንዮን ደቡብ ማዕከላዊ እስያ ውስጥ (አሁን ቱርክ ያለችበት) የምትገኝ ከተማ ነበረች።
ኢትዮጵያ ከግብፅ በስተደቡብ ያለች አፍሪካዊት አገር ስትሆን፣ በስተምዕራብ የአባይ ወንዝ፣ በስተምሥራቅ ደግሞ ከቀይ ባሕር ጋር ትዋሰናለች። ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ ሰው ኢትዮጵያዊ ይባላል።
ኢየሩሳሌም በኋላ እጅግ ተፈላጊ የሆነች በመጀመሪያ የከነዓናውያን የነበረች ጥንታዊት ከተማ ነበረች። አሁንም ኢየሩሳሌም የዘመናዊት ኢየሩሳሌም ዋና ከተማ ነች።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዩ ተብለው የሚጠሩ ሁለት ሰዎች አሉ።
ኢያሪኮ በተስፋው ምድር በከነዓን የነበረች በጣም ኅያል ከተማ ነበረች።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢያሱ በመባል የሚታወቁ በርካታ ሰዎች አሉ። በጣም ታዋቂው የነዌ ልጅና የሙሴ ረዳት የነበረው በኋላም የእግዚአብሔር ሕዝብ ሁነኛ መሪ የሆነው ኢያሱ ነበር።
ኢያቡሳውያን፤ ያቡስ ከሚባል ሰው የተወለዱ በከነዓን የነበሩ ነገድ ናቸው።
ኢይዝራኤል ከጨው ባሕር ደቡብ ምዕራብ ነገድ ክልል ውስጥ የነበረች በጣም ጠቃሚ የእስራኤል ከተማ ስም ነው። ጥቂት የእስራኤል ንጉሦች ቤተመንግሥታቸውን የሠሩት እዚያ ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮራም ተብለው የሚጠሩ ሁለት ንጉሦች ነበሩ።
ኢዮራም የእስራኤል ንጉሥና የአክዓብና የኤልዛቤል ልጅ ነበር።
የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም ከ900-910 ዓቅክ ገደማ የሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት የመጀመሪያው ንጉሥ ነበር። ኢዮርብዓም የሚባል ሌላው ንጉሥ የኢዮአስ ልጅ ሲሆን ከ120 ዓመት በኋላ እስራኤልን ገዝቷል። አንዳንዴ፣ “ቀዳማዊ ኢዮርብዓም” እና “ዳግማዊ ኢዮርብዓም” ይባላሉ።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮሳፍጥ ቢያንስ የሁለት ሰዎች ስም ነበር።
ኢዮስያስ ለሰላሳ እንደ ዓመት የይሁዳን መግሥት የገዛ እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጉሥ ነበር። ሕዝቡ በንስሐ እንዲመለሱና ያህዌን እንዲያመልኩ ለማበረታታት ብዙ ነገሮች አድርጓል።
ኢዮብ፣ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅና በደል የሌለበት እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገርለት ሰው ነው። የበለጠ የሚታወቀው ታላቅ ስቃይና ሐዘን ቢደርስበትም በእግዚአብሔር በነበረው እምነት በመጽናቱ ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮአስ ተብለው የሚጠሩ ጥቂት ሰዎች ነበሩ።
ኢዮአቄም የይሁዳን መንግሥት ከገዙ ንጉሦች አንዱ ነበር።
ኢዮአቄም ከ60 ዓቅክ ጀምሮ በይሁዳ መንግሥት ላይ የነገሠ በጣም ክፉ ነጉሥ ነበር። እርሱ የንጉሥ ልጅ ነበር። መጀመሪያ ላይ ኤልያቄም ይባል ነበር።
ኢዮአብ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ የንጉሥ ዳዊት ሁነኛ የጦር መሪ ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮአታም ተብለው የሚጠሩ ሦስት ሰዎች አሉ።
ኢዮኤል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለውን ትንቢተ ኢዮኤል የጻፈ ነብይ ነበር፤ ትንቢተ ኢዮኤል የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ክፍል ከሆኑት አሥራ ሁለት አጫጭር ትንቢቶች አንዱ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ኢዮጴ ከተማ ከኢየሩሳሌም ሰሜናዊ ምዕራብ 30 ማይሎች ርቃ ሜድትራንያን ባሕር ላይ የምትገኝ በጣም ጠቃሚ የንግድ ባሕር ወደብ ነበረች።
ኤላም የሴም ልጅ፣ የኖኅ የልጅ ልጅ ነው።
ኤልሳቤጥ የመጥምቁ ዮሐንስ እናት ናት። የባልዋ ስም ዘካርያስ ነበር።
ኤልያስ አክዓብን፣ አካዝያን፣ ኢዮራምን፣ ያሑን፣ ኢዮአስንና ዮአስን በመሳሰሉ በርካታ የእስራኤል ነገሥታት ዘመን ነበር ያገለገለው።
ኤልዛቤል ዐመፀኛዋ የእስራኤል ንጉሥ የአክአብ ሚስት ነበረች።
ኤልያስ በጣም ታዋቅ ከሆኑት የያህዌ ነቢያት አንዱ ነበር። ንጉሥ አክዓብን ጨምሮ ኤልያስ በተለያዩ የእስራኤል ወይም የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ነበር ያገለገለው።
ኤልያቄም የሁለት የብሉይ ኪዳን ሰዎች ስም ነው።
ኤሞር አይሁዳዊ ያልነበረ የያዕቆብ ጎረቤት የነበረ ሰው ነው።
ኤርምያስ በይሁዳ መንግሥት የእግዚአብሔር ነብይ ነበር።
ኤሳው ይስሐቅ ከርብቃ ከወለደቻቸው መንታ ልጆች ታላቁ ነበር፣ መንታ ወንድሙ ያዕቆብ ነበር።
ምድሪቱን እንዲወርሱ ኢያሱ እስራኤላውያንን እየመራ በወሰደ ጊዜ ኤዊያውያን በከነዓን ምድር ከነበሩ ሰባት ዋና ዋና ሕዝቦች አንዱ ነበሩ።
በጥንት ዘመን ኤደን እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ወንድና ሴት ያኖረበት የአትክልት ቦታ ያለው አካባቢ ነበር።
ኤዶም፣ የኤሳው ሌላው ስም ሲሆን፣ ኤዶማውያን የእርሱ ዘሮች ናቸው። የኤዶም አገር ኤዶምያ ወይም ሴይር በመባልም ይታወቃል።
ኤፌሶን በአሁኑ ዘመን ቱርክ በምትባለው አገር ምዕራባዊ ባሕር ዳርቻ የነበረች ጥንታዊ የግሪክ ከተማ ነበረች።
ኤፍራጥስ በኤደን የአትክልት ቦታ ውስጥ ያልፉ ከነበሩ አራት ወንዞች አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተደጋጋሚ የተጠቀሰ ወንዝ ነው፣ አንዳንዴ፣ “ወንዙ” በመባል በአጭር ቃል ተጠርቷል።
ኤፍሬም የዮሴፍ ሁለተኛ ልጅ ነው። የእርሱ ዘር የሆኑት ኤፍሬማውያን አስራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ከተሰባሰቡባቸው አንዱ ሆኗል።
እሴይ የቦዔዝ የልጅ ልጅና የንጉሥ ዳዊት አባት ነው።
እስማኤል የአብርሃምና የሥራ አገልጋይ የነበረችው የአጋር ልጅ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፥ “እስያ” የሮም መንግሥት አውራጃ ስም ነበር። በአሁኑ ጊዜ ቱርክ ከሚባለው አገር ምዕራባዊ ክፍል ነበር የሚገኘው።
እስጢፋኖስ የመጀመሪያው ክርስቲያን ሰማዕት ማለትም በኢየሱስ በማመኑ የተገደለ የመጀመሪያ ሰው በመሆኑ ይበልጥ ይታወቃል። ሕይወቱንና አሟሟቱን የሚያመለክት ዝርዝር ሐዋርያት ሥራ የተሰኘው መጽሐፍ ውስጥ ተጽፏል
ኦርዮን ጻድቅ ሰውና ከንጉሥ ዳዊት ምርጥ ወታደሮች አንዱ ነበር።
ከለድ የመስጶጤምያ ወይም የባቢሎን ደቡባዊ ክፍል የነበረ ቦታ ነበር። በዚህ ቦታ የነበሩ ስዎች ከለዳውያን ይባሉ ነበር።
ከሊታውያን ምናልባት የፍልስጥኤም አካል የነበሩ ሕዝብ ነበሩ።
ከነዓን የኖኅ ወንዶች ልጆች አንዱ የነበረው የካም ልጅ ነበር። ከነዓናውያን የከነዓን ዘሮች ናቸው።
ኩሽ የኖኅ ልጅ ካም ትልቁ ልጅ ነበር። የናምሩድ ጥንተ አባትም ነበር። ሁለቱ ወንድሞቹ ግብፅና ከነዓን ነበር።
ኪልቅያ አሁን የዘመኑ ቱርክ ካለችበት ደቡብ ምሥራቃዊ ክፍል የነበረች አነስተኛ የሮማውያን አውራጃ ነበረች። ከኤጂያን ባሕር ጋር ይዋሰናል።
ካሌብ የከነዓንን ምድር እንዲሰልሉ ሙሴ ከላካቸው አሥራ ሁለት እስራኤላውያን አንዱ ነበር።
ካም ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሱት ሦስቱ የኖኅ ልጆች ሁለተኛው ነው።
ኬልቅያስ በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን የነበረ ሊቀ ካህን ስም ነው።
ኬብሮን ከኢየሩሳሌም ደቡብ 20 ማይሎች ርቀት ላይ ያለች ከፍታ ያለው ዐለታማ ኮረብታላይ የምትገኝ ከተማ ናት።
ኬጢያውያን በልጁ በከነዓን በኩል የካም ዘሮች ነበር። በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለውና ከፐስቲና በስተ ሰሜን ባለው አካባቢ ታላቅ መንግሥት ሆነው ነበር።
የኮሬብ ተራራ አሥሩ ትእዛዞች የተጻፈባቸው ሁለት የድንጋይ ጽላቶችን እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠበት የሲና ተራራ ሌላ ስም ነው።
ዐባይ ወንዝ በሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ በጣም ረጅምና ሰፊ ወንዝ ነው።
ዑር በጥንቱ ከለድያ አካባቢ ኤፍራጥስ ወንዝ ዳር የነበረ ጠቃሚ ከተማ ሲሆን የሚገኘው በዚህ ዘመን ኢራቅ በሚባለው አገር ውስጥ ነው።
በብሉይ ኪዳን ዘመን ዓረባ የሚለው አገልላለጽ በዮርዳኖስ ወንዝ ዙሪያ በስትደቡብ ወደ ሰሜናዊ የቀይ ባህር ጫፍ የሚዘረጋ የነበረውን ሸለቆ ጨምሮ በጣም ስራ በረሐ ለጥ ያለ ሜዳ ያመለክታል።
ዓይንጋዲ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምሥራቅ ይሁዳ ምድረ በዳ ላይ የምትገኝ ከተማ ስማ ነው።
ዕንባቆም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት የነበረ የብሉይ ኪዳን ነቢይ ነው።
ዕዝራ እስራኤላዊ ካህንና የአይሁድ ሕግ ሊቅ ነበር፤ ለ70 ዓመት በባቢሎን ምርኮ ከኖሩ በኋላ ወደኢየሩሳሌም የተመለሱ እስራኤላውያንን ታሪክ በጽሁፍ ያሰፈረ እርሱ ነበር።
ዖምሪ በኋላ ስድስተኛው የእስራኤል ንጉሥ የሆነ የጦር አዛዥ ነበር።
በ800 ዓቅክ ዖዝያ በ16 ዓመቱ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ፤ ለ52 ዓመት በኢየሩሳሌም ነገሠ፤ ይህ በጣም ረጅም ዘመን ነበር። ዖዝያ “አዛርያስ” ተብሎም ይጠራል።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዘሩባቤል ተብለው የተጠሩ ሁለት ሰዎች ነበር።
ዘብድዎስ ዓሣ አጥማጅ የገሊላ ሰው ነበር። ያዕቆብና ዮሐንስ የተባሉ ሁለት ልጆቹ አብረውት ይሠሩ ነበር። በኋላ ግን ሥራቸውን ትተው ሁለቱም የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ።
ዘካርያስ በኋላ መጥምቁ ዮሐንስን የወለደ የአይሁድ ካህን ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዘካርያስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ሰዎች ነበሩ። ከእነርሱም ዋና ዋናዎቹ፣
ዘኬዎስ የኢያሪኮ ሰው ሲሆን፣ በጣም የሚታወቀው ኢየሱስን ለማየት ዛፍ ላይ በመውጣቱ ነው።
ዘዓር እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን ሲያጠፋ ሎጥ ሮጦ ያመለጠባት ትንሽ ከተማ ነበረች።
ዛብሎን የያዕቆብና የልያ የመጨረሻ ልጅ ሲሆን፣ ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች የአንዱ ስም ነበር።
ንጉሥ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን በሁለት መንግሥታት ተከፈሉ። የእስራኤል መንግሥት አሥሩን ነገዶች የያዘው ሰሜናዊ መንግሥት ነበር።
የእግዚአብሔር ሰው የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር የያህዌ ነቢይ በአክብሮት የሚጠራበት ቃል ነው።
“የዳዊት ቤት” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር የንጉሥ ዳዊትን ቤተ ሰብ ወይም ዘር ያመለክታል።
“የዳዊት ከተማ” የኢየሩሳሌምና የቤተልሔም ሌላው ስም ነው።
የገሊላ ባሕር ምሥራቃዊ እስራኤል ያለ ሐይቅ ነው። የገሊላ ባሕር በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ወደ ደቡብ ከዚያም ወደ ሙት ባሕር ይፈስሳል።
ሙት ባሕር ተብሎም የሚጠራው የጨው ባሕር የሚገኘው በምዕራብ በኩል ከእስራኤል በስተደቡብና በምሥራቅ በኩል ከሞአብ መካከል ነው
ያዕቆብ የማርያምና የዮሴፍ ልጅ ሲሆን፣ ከኢየሱስ ግማሽ ወንድሞች አንዱ ነበር።
የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር።
የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ዮሐንስ የሚባል ታናሽ ወንድም የነበሩት ሲሆን፣ እርሱም ከኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር።
ያዕቆብ የይስሐቅና የርብቃ ታናሹ መንታ ልጅ ነው።
ያፌት ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሱት ሦስቱ የዮኅ ልጆች አንዱ ነው።
ይሁዳ የያዕቆብ አራተኛ ልጅ ነው እናቱ ልያ ትባላለች።
“ይሁዳ” የሚለው ቃል የመጣው ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ከነበረው ይሁዳ ከሚለው ስም ነው። ጠበብ ባለና ሰፋ ባለ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።
ተርጓሚዎቹ ልዩነቱን በጣም ግልጽ ማድረግ ከፈለጉ፣ ሰፋ ባለ መልኩ የቀረበውን ይሁዳ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥5) “የይሁዳ አገር” በማለት መተርጎም ይችላሉ፤ ጠበብ ባለ መልኩ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥39) ጥቅም ላይ ከዋለ፣ ይህ ቦታ መጀመሪያ የይሁዳ ነገድ የነበረበት የጥንቱ የእስራኤል ምድር አካል ስለነበር፣ “የይሁዳ ክፍለ ሀገር” በማለት መተርጎም ይቻላል።
የያዕቆብ ልጅ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ደቀመዛሙርት አንዱ ነበር። ይኸኛው ከአስቆሮቱ ይሁዳ የተለየ መሆኑን ልብ በሉ።
የአይሁድ ሕዝብ የሚለማመደውን ሃይማኖት ማለትም የአይሁድ ሃይማኖትን ለማመልከት አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ዘመን አንስቶ እስከዚህ ዘመን ድረስ፣ “ይሁዲ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።
ይሳኮር የያዕቆብ ማለትም የእስራኤል ዘጠነኛ ልጅ ነው።
ምንም እንኳ በጣም ያረጁ ቢሆኑም ለእነርሱ እንደሚሰጣቸው እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለሣራ ቃል የገባላቸው ልጅ ነው።
ዮሐንስ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት እንዱ ነበር፤ ከኢየሱስ የቅርብ ወዳጆችም አንዱ ነበር።
ዮሐንስ የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ነበር። ዮሐንስ የተሰኘው ስም በጣም የተለመደ ከመሆኑ የተነሳ ሐዋርያው ዮሐንስን ከመሳሰሉ ዮሐንስ ከተባሉ ሌሎች ሰዎች እርሱን ለመለየት፣ “መጥምቁ ዮሐንስ” ተብሏል።
ዮሐንስ ማርቆስ በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር ከተጓዙ ሰዎች አንዱ ሲሆን፣ ማርቆስ ተብሎ ይጠራል።
ዮርዳኖስ ወንዝ ከሰሜን ወደደቡብ፣ ከነዓን ተብሎ ይጠራ ከነበረው ምድር ምሥራቃዊ ድንበር ይፈስ የነበረ ወንዝ ነው።
ዮሴፍ የያዕቆብ አሥራ አንደኛ ልጅ ሲሆን፣ ለራሔል ደግሞ የመጀመሪያ ልጇ ነበር።
ዮሴፍ የማርያም እጮኛ የነበረ ሲሆን፣ እንደ አባት ኢየሱስን አሳድጓል።
ዮቶር እና ራጉኤል የተሰኙት ስሞች የሚያመለክቱት የሙሴን ሚስት የሴፎራን አባት ነው። ራጉኤል የጎሳው ስም ሊሆን ይችላል።
ዮናስ በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ እስራኤላዊ ነቢይ ነበር።
ዮናታን ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል። ትርጉሙ፣ “ያህዌ ሰጥቷል” ማለት ነው።
ዮዳሔ ንጉሥ ለመሆን እስከበቃበት ድረስ የንጉሥ አካዝያስን ልጅ ኢዮአስን ደብቆ ያቆየውና የተከላከለለት ካህን ነበር።
ዮፍታሔ የእስራኤል መስፍን ወይም ገዢ በመሆን ያገለገለ ከገለአድ የመጣ ጦረኛ ነበር።
ደሊላ ሚስቱ ባትሆንም ሳምሶን ወዶአት የበረች ፍልስጥኤማዊት ናት።
ደማስቆ ሶርያ የሚባለው አገር ዋና ከተማ ነው። ዛሬም ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበረበት ቦታ ላይ ነው ያለው።
ደብረ ዘይት ተራራ ከኢየሩሳሌም ከተማ በስተ ምሥራቅ በኩል ያለ ተራራ ወይም ረጅም ኮረብታ ነው። ይህን ስሙን ያገኘው በብዛት እዚያ ከሚገኙት የወይራ ዛፎች ሊሆን ይችላል።
“ደንገል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ውሃ ውስጥ፣ ብዙውን ጊዜም ወንዝ ወይም ምንጭ ዳር የሚበቅል ረጅም አገዳ ያለው ተክል ነው።
ዳርዮስ የበርካታ የፋርስ ነገሥታት ስም ነው። “ዳርዮስ” የማንነት መገለጫ እንጂ መጠሪያ ስም አይደለም።
ዳን አምስተኛው የያዕቆብ ልጅ ሲሆን ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ነበር። የዳን ነገድ ይኖርበት የነበረው ሰሜናዊው የከነዓን ክፍል በዚህ ስም ይጠራል።
ዳንኤል ገና ወጣት እያለ በ600 ዓቅክ በባቢሎን ነጉሥ ናቡከደነፆር በምርኮ የተወሰደ እስራኤላዊ ነቢይ ነበር።
ዳዊት እግዚአብሔርን በመውደዱና እርሱን በማገልገሉ የታወቀ ሁለተኛው የእስራኤል ንጉሥ ነው። የመዝሙራት መጽሐፍ ዋናው ጸሐፊም እርሱ ነው።
ገለዓድ የጋድ፣ የሮቤልና የምናሴ ነገዶች የነበሩበት ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ የነበረ ተራራማ አካባቢ ስም ነው።
ገሊላ ከሰማርያ እንኳ በጣም ርቆ ሰሜናዊ የእስራኤል ጫፍ አካባቢ ነበረች።
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ገላትያ በአሁኑ ዘመን ማዕከላዊ ቱርክ የሚባለው ቦታ ላይ ትገኝ የነበረች የሮም ከተማ ነበረች።
ገባኦን፣ ገባኦናውያን የሚኖሩባት ምድረ ከነዓን ውስጥ የነበረች ከተማና አካባቢ ናት።
ገብርኤል ከእግዚአብሔር መላእክት የአንዱ ስም ነው።
ጊብዓ ከኢየሩሳሌም በስተ ሰሜንና ከቤቴል በስተ ደቡብ የነበረ ከተማ ስም ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጋዛ የሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ፣ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምዕራብ 77 ኪሎ ሜትር፣ ከአሽዶድ በስተ ሰሜን 38 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች በጣም አስፈላጊ የፍልስጥኤማውያን ከተማ ነበረች።
በብሉይ ኪዳን ዘመን ጋይ ከቤቴል በስተ ደቡብ ከኢያሪኮ ሰሜን ምዕራብ 8 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የምትገኝ የከነዓናውያን ከተማ ስም ነበረች።
ጋድ ከያዕቆብ ማለትም ከእስራኤል ልጆች የአንዱ ስም ነው። የጋድ ቤተሰብ ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ሆነዋል።
ጌልጌላ ከኢያሪኮ በስተ ሰሜን ያለች አገር ስትሆን፣ ወደ ከነዓን ለመግባት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ወንዝ ከተሻገሩ በኋላ የሰፈሩባት የመጀመሪያ ቦታ ናት።
ጌሣም ከግብፅ ሰሜናዊ ክፍል አካባቢ የሚገኝ ቦታ ስም ነበር።
ጌራራ ምድረ ከነዓን ውስጥ የነበረ ከተማና አካባቢ ሲሆን፣ ከኬብሮን ደቡብ ምዕራብና ከቤርሳቤህ ሰሜን ምዕራብ ይገኝ ነበር።
ጌርሳውያን የኖኅ ልጅ የካም ልጅ የሆነው የከነዓን ዘሮች ይኖሩበት በነበረው ምድረ ከነዓን የነበሩ ነገድ ናቸው።
በንጉሥ ዳዊት ዘመን ጌሸር ከገሊላ ባሕር በስተ ምሥራቅ በኩል፣ በእስራኤልና በአራም አገሮች መካከል የነበረች ታናሽ መንግሥት ነበረች።
ጌቴሴማኒ ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ ከቄድሮን ሸለቆ ማዶ፣ ደብረ ዘይት ተራራ አጠገብ ያለ የወይራ ዛፎች የነበሩበት አትክልት ቦታ ነው።
ጌት ከአምስቱ የፍልስጥኤም ዋና ዋና ከተሞች አንዷ ነበረች። የምትገኘው ከአቃሮን በስተ ሰሜንና ከአሾዶድና ከአስቄሎና በስተ ምሥራቅ ነበር።
ጌዶዎን እስራኤልን ከጠላቶቻቸው እንዲያድን እግዚአብሔር ያስነሣው እስራኤላዊ ነው።
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ግሪክ የሮም መንግሥት ግዛት ውስጥ ያለች አገር ነበረች።
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ግሪክኛ በግሪክና በመላው የሮም መንግሥት ብዛት መግባቢያ ቋንቋ ነበር፤ የመጀመሪያው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት በግሪክኛ ነበር።
ግብፅ ከአፍሪካ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል፣ ከምድር ከነዓን ደቡብ ምዕራብ የምትገኝ አገር ነች።
ጎልያድ ዳዊት በወንጭፍ ድንጋይ የገደለው ግዙፍ ፍልስጥኤማዊ ወታደር ነበር።
“ጎልጎታ” ኢየሱስ የተሰቀለበት ቦታ ስም ነው። ቃሉ የመጣው፣ “የራስ ቅል” ወይም፣ “የራስ ቅል ቦታ” ከተሰኙ የአረማይክ ቃል ነው።
ጎሞራ ከባቢሎንያ አካባቢ በስተ ምሥራቅ ባለው በጣም ለም ሸለቆ ውስጥ አንድ ቦታ ላይ የነበረች ከተማ ነበረች።
ጎቶልያ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮራም ሚስት ስትሆን፥ በጣም ክፉ ሴት ነበርች። በክፋቱ የታወቀው የእስራኤል ንጉሥ የዘምሪ የልጅ ልጅ ነበረች
ጠርሴስ በአሁኑ ዘመን ማዕከላዊ ደቡብ ቱርክ ባለበት የሮም ኪልቂያ አውራጃ ውስጥ የነበረች ጥንታዊ ሀብታም ከተማ ናት
ጢሞቴዎስ እርሱ በነበረበት ልስጥራ ከተማ ጳውሎስ ባገለገለ ጊዜ በክርስቶስ ያመነ ወጣት ሰው ነበር። በኋላም ጳውሎስ ባደረገው በርካታ ሐዋርያዊ ጉዞ አብሮት ነበር፤ የአዲስ አማኞች ማኅበረ ሰብ መጋቢ በመሆንም አገልግሏል።
ጢሮስ በአሁኑ ዘመን ሊባኖስ በሚባለው ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ ላይ የነበረች ጥንታዊ የከነዓናውያን ከተማ ናት። የከተማዋ አንድ ክፍል ከባሕሩ ዳርቻ አንድ ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገባ ካለው ደሴት ጋር ይያያዛል።
የጢሮአዳ ከተማ በጥንቱ የሮም እስያ አውራጃ ሰሜን ምዕራብ ባሕር ዳርቻ ትገኝ የነበረች ወደብ ናት።
ጤባርዮስ ቄሳር ኢየሱ ባገለገለበት ዘመን ይሁዳን እየገዛ የነበረ ሮማዊ ነው። ምንም እንኳ በእርግጥ ንጉሥ ባይሆንም አንዳንዴ “ንጉሥ ሄሮድስ” እየተባለ ይጠራል።
ጲላጦስ ኢየሱስ እንዲገደል የፈረደ ሮማዊ ባለ ሥልጣን ነበር።
ጳርቴ ወይም ጳንጦስ በሮም መንግሥትና በጥንት ቤተ ክርስቲያን ዘመን የሮም አውራጃ ነበረች። የምትገኘው በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለው ሰሜናዊ ክፍል ጥቁት ባሕር ዳርቻ ነበር።
ጳውሎስ ለሌሎች ብዙ ሕዝቦች የምሥራቹን ቃል እንዲያደርስ ኢየሱስ የላከው የጥንት ቤተ ክርስቲያን መሪ ነበር።
እነዚህ ስሞች ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ የነበረው የጴጥሮስ መጠሪያዎች ናቸው። በጥንት ቤተ ክርስቲያን ታዋቂ መሪ ነበር።
ያዕቆብና ሚስቶቹ እንዲሁም ልጆቹ በከነዓን ምድር በነበሩ ጊዜ ጴጥፍራ የግብፅ ፈርዖን ከፍተኛ ባለ ሥልጣን ነበር። ጴጥፍራ የዘቦች አለቃ ነበር።
ኀይል፣ ኀይላት “ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።
ጵርስቅላ ከባልዋ ከአቂላ ጋር በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር አብራ ትሠራ የነበረች የመጀመሪያው መቶኛ ዓመት አይሁዳዊት ክርስቲያን ነበረች።
በጥንት ዘመን ግብፅን ይገዙ የነበሩ ንጉሦችን ፈርዖን ነበር።
ፊልጵስዩስ በጥንቷ ግሪክ ሰሜናዊ ክፍል ትገኝ የነበረች ከተማ ናት።
ሐዋርያው ፊልጶስ ከመጀመሪያዎቹ አሥራ ሁለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ነበር።
በኢየሩሳሌም በነበረችው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ፊልጶስ ለድኾችና ችግረኛ ክርስቲያኖች በተለይም ለመበለቶች ጥንቃቄ እንዳይደርጉ ከተመረጡ ሰባት መሪዎች አንዱ ፊልጶስ ነበር።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ፊንሐስ ተብለው የተጠሩ ሁለት ሰዎች አሉ።
በጥንት ዘመን ፊንቂያ ሜዲትራንያን ባሕር ዳር የምትገኝ በጣም ሀብታም ከተማ ነበረች። የአሁኗ ሊባኖስ ካለችበት ምዕራብ አካባቢ ነበር የምትገኘው።
የፋራን በረሐ ከግብፅ በስተምሥራቅና ከምድረ ከንዓን በስተደቡብ የሚገኝ ምድረበዳ ነበር። ፋራን የሚባል ተራራም ነበር፤ ምናልባትም ይህ ስም የሲና ተራራ ሌላ ስም ሊሆን ይችላል።
ፋርስ በ550 ዓቅክ ታላቁ ቂሮስ የመሠረተው መንግሥት ነው። ማዕከሉ የነበረው የአሁኗ ዘመን ኢራን ያለችበት ቦታ ላይ ነበር። የፋርስ ነዋሪዎች፣ “ፋርሳውያን” ይባላሉ።
ፌርዛውያን በፓለስቲና ከነበሩ እስራኤላውያን ጋር ብዙ ውጊያ ያደረጉ፣ “ብሔር” ነበሩ። ስለ ማንነታቸው ወይም የት ይኖሩ እንደ ነበር ምንም ገለጻ አልተሰጠም።
ፌፎር ከጨው ባሕር በስተ ምሥራቅ ሞዓብ ምድር ውስጥ የሚገኝ ተራራ ስም ነው። የሮቤል ነገድ የሚኖረው እዚህ ነበር።
ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም በመባል በሚታወቀው የሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው። የስማቸው ትርጕም፣ “የባሕር ሰዎች” ማለት ነው።
ፍልስጥኤም ምድረ ከነዓን ውስጥ በጣም ሰፊ የነበረው አካባቢ ስም ሲሆን፣ የምትገኘው በሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ ነበር።
ፔዳን አራም ወደ ምድረ ከንዓን ከመሄድ በፊት የአብርሃም ቤተሰብ የነበረበት ቦታ ነው።