ምዕራፍ 41

1 ለድሆች የሚያስቡ እንዴት የታደሉ ናቸው፣ ችግር በገጠማቸው ጊዜ እግዚአብሔር ይታደጋቸዋል። 2 እግዚአብሔር ይጠብቃቸዋል፣ ረጅምን እድሜ ይሰጣቸዋል። በእስራኤል ምድር ደስተኞች እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፣ ከጠላቶቻቸውም ይታደጋቸዋል 3 በታመሙ ጊዜ ይፈውሳቸዋል፣ ያጠነክራቸዋልም። 4 እኔ በታመምኩ ጊዜ፣ እንዲህ አልኩ፣ “እግዚአብሔር ሆይ በምሕረትህ ተመልከተኝ ፈውሰኝም፣ በአንተ ላይ ኃጢአትን ከማድረጌ የተነሣ መታሜን አውቃለሁና። 5 ጠላቶቼ በእኔ ላይ ክፉ ነገር ተናገሩ፣ እንዲህ አሉ፣ ሁሉም ሰው እንዲረሳው በቶሎ እንዴት ይሞታል?” 6 ጠላቶቼ ወደ እኔ ሲመጡ፣ ስለ እኔ እንደሚያስቡ በማስመሰል ተናገሩ። ስለ እኔ ያለውን ክፉ ወሬ ሁሉ ግን በጉጉት ይሰሙ ነገር። ከዚያም ሄደው ለሰው ሁሉ በእኔ ላይ የደረሰውን ተናገሩ። 7 የሚጠሉኝ ሁሉ በእኔ ላይ አንሾካሾኩ፣ በእኔ ላይ አንሾካሾኩ፣ በእኔ ላይ ክፉ ነገር እንዲደርስብኝ ተስፋ አደረጉ። 8 እንዲህም አሉ፣ “ስለታማመ በቶሎ ይሞታል፣ ከተኛበት አልጋ ፈጽሞ ሊነሣ አይችልም።” 9 የቅርብ ጓደኞቼ እንኳን፣ እጅግ የማምናቸውና ብዙ ጊዜ ከእኔ ጋር የሚሆኑ አሳልፈው ሰጡኝ። 10 ነገር ግን፣ እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔን በምሕረትህ አስበኝ፣ እንደገና ጤነኛ እንድሆን አስችለኝ። ይህን ብታደርግልኝ ለጠላቶቼ እመልስላቸዋለሁ። 11 ጠላቶቼ እንዳያሸንፉኝ ብታደርገኝ፣ በእኔ ደስ እንደተሰኘህ በዚህ አውቃለሁ። 12 እኔ በቅንነቴ እውነትን ስላደረግሁ እንደረዳኸኝ አውቃለሁ፣ ከአንተም ጋር ለዘላለም እንድሆን እንዳስቻልከኝም አውቃለሁ። 13 እኛ እስራኤላውያን የምናመልክህ፣ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ፣ ተመስገን፤ ለዘላለም አምስግኑት! አሜን! ለዝላለም ይህ ይሆን ዘንድ ምኞቴ ነው።