ምዕራፍ 72

1 አምላክ ሆይ፣ እስራኤል ላይ የሾምኸው ንጉሥ በጽድቅ እንዲፈርድ አብቃው፡፡ በፍትሕ እንዴት እንደሚፈርድ አሳየው፡፡ 2 በሕዝብህ ላይ በፍትሕ መፍረድ እንዲችል፤ የረጨቆኑትን ሕዝብህን በትከክል እንዲያስተዳድር አሳየው፡፡ 3 አገሪቱ ሁሉ በተራራዎችና በኮረብታዎች እንኳ ሕዝቡ በሰላምና በጽድቅ ይኖራል፡፡ 4 ለድኾች እንዲፈርድ ንጉሥህን እርዳው፤ እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን እንዲያድንና የጨቆኑአቸውን እንዲያሸንፍ እርዳው፡፡ 5 ንጉሥህ በዘመናት ሁሉ የፀሐይና የጨረቃን ያህል ረጅም ዘመናት እያበራ ለዘለዓለም እንዲኖር እፈልጋለሁ፡፡ 6 ንጉሡ መስክ ላይ በሚዘንብ ዝናብ እንደሚያድግ ሰብል፣ በምድርም ላይ እንደሚወርድ ጠል በእርሱ አመራር ሕዝቡ ደስ እንዲሰኙ እፈልጋለሁ፡፡ 7 በእርሱ የግዛት ዘመን እንደሚኖሩ፤ እንደ ጨረቃ በሰላምና በብልጽግና ሕዝቡ እንደሚኖር ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ 8 የእስራኤል ንጉሥ ግዛቱ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከኤፍጥስ ወንዝ እስከ ምድር ዳርቻ ይድረስ ይሆናል፡፡ 9 በበረሃ የሚኖሩ በፊቱ ይስግዳሉ፤ ጠላቶቹም ወደ መሬት ወድቀው ለንጉሣችን እጃቸውን ለመስጠት ይሰግዳሉ፡፡ 10 የተርሴስ ደሴቶች ነገሥታት ስጦታ ያቅርባሉ፤ የሳባና የዐረብ ነገሥታት እጅ መንሻ ያመጡለታሉ፡፡ 11 የዓለም ነገሥታት ሁሉ ለእስራኤል ንጉሥ ይሰግዱለታል፤ ሕዝቦችም ሁሉ ንጉሣችንን ያገልግሉታል፡፡ 12 ለእርዳታ ወደ እርሱ የሚጮኹትን ድኾች ያድናቸዋል፤የሚረዳቸው የሌላቸውን ችግረኞችንና የተጨቆኑትን ሰዎች ይረዳቸዋል፡፡ 13 ለደኾችና ለደካሞች ይራራል፤ በችግር ላይ ያትንም ሰዎች ከሞት ያድናል፡፡ 14 ንጉሣችን ከጭቆናና ከጭካኔ አገዛዝ ያድናቸዋል፤ ለንጉሣችን የእነርሱ ሕይወት ውድ ስለ ሆነ ነው፡፡ 15 ንጉሡ ረጅም ዘመን ይኖራል፤ ከሳባም ወርቅ ይመጣለታል፤ ስለ እርሱም ዘወትር ጸሎት ይደረጋል፤ሰዎችም ሁልጊዜ በየቀኑ ያመሰግኑታል፡፡ 16 በሊባኖስ ተራራ እንደሚበቅል ሰብል በምድሩቱ ተራራዎች ራስ ሳይቀር በሁሉም መስኮች ብዙ ሰብሎችን ያፈራሉ፤ መስኮች በሣር እንደሚሸፈን የእስራኤል ከተሞች በሕዝብ ይሞላሉ፡፡ 17 የንጉሡም ስም ለዘለዓለሙ ሲታወስ ይኑኖራል፤ ሕዝቡም ፀሐይ እያበራ እንደሚኖር ለዘመን ሁሉ ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ ልክ የእስራኤልን ንጉሥ ስለባረከው፣ ሕዝብ ሁሉ የእስራኤልን አምላክ፣ ያህዌን ያመሰግናሉ፡፡ 18 እኛ እስራኤላውያን የምናመልከው፣ ያህዌ ይመስገን፤ እርሱ ብቻ ተአምትን የሚያደርገው፡፡ 19 እርሱ ለዘለዓለም ይመስገን፤ የእርሱ ዓለምን ሁሉ ይሞላል፡፡ አሜን! እንዲሁም ይሁን! 20 ይህ የእሴይ ልጅ የዳዊት ጸሎት ፍጻሜ ነው፡፡