ምዕራፍ 1
1
ክፉዎች እንዲያደርጉ የሚመክሩአቸውን የማያደርጉ፣ የኃጢአተኞችን ባሕርይ እንዲሁም በእግዚአብሔር የሚያሾፉትን ሰዎቸ የማይከተሉ ምንኛ የታደሉ ናቸው?
2
ይልቁንም፣ ያሕዌ ደስ የሚሰኝባቸው እርሱ የሚያስተምረንን በሚረዱና በዚያም ደስ በሚላቸው ነው፡፡
3
እነርሱ ሁልጊዜ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ያደርጋሉ፡፡ በወንዝ ዳር እንደተተከለ ፍሬውንም በየዓመቱ በትክክለኛው ጊዜ እንደሚሰጥ ቅጠሉም እንደማይግፍ ዛፍ ናቸው፡፡ የሚሠሩት ሁሉ ይከናወንላቸዋል፡፡
4
ክፉ ሰዎች ግን እንደዚህ አይደሉም፣ ክፉ ሰዎች ከዛፍ እንደሚራገፉና ነፋስም ጠርጎ እንደሚወስዳቸው እንደማይጠቅሙ ገለባዎች ናቸው፡፡
5
ስለዚህ፣ እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ በሚፈርድበት ጊዜ፣ ክፉዎችን ይኮንናቸዋል፡፡ ከዚህም ሁሉ በላይ፣ ያሕዌ ዱሳንን በአንድ ላይ በሚሰበስብበት ጊዜ፣ ክፉዎች በዚያ ሊገኙ አይችሉም፡፡
6
ያሕዌ ቅዱሳንን ይመራቸዋል ይጠንቃቸዋልም፤ ክፉዎች የሚሄዱበት መንገድ ግን እግዚአበሔር እነርሱን ለዘላለም ወደሚየጠፋበት አቅጣጫ ይወስዳቸዋል፡፡