ምዕራፍ 1

1 ክፉዎች እንዲያደርጉ የሚመክሩአቸውን የማያደርጉ፣ የኃጢአተኞችን ባሕርይ እንዲሁም በእግዚአብሔር የሚያሾፉትን ሰዎቸ የማይከተሉ ምንኛ የታደሉ ናቸው? 2 ይልቁንም፣ ያሕዌ ደስ የሚሰኝባቸው እርሱ የሚያስተምረንን በሚረዱና በዚያም ደስ በሚላቸው ነው፡፡ 3 እነርሱ ሁልጊዜ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ያደርጋሉ፡፡ በወንዝ ዳር እንደተተከለ ፍሬውንም በየዓመቱ በትክክለኛው ጊዜ እንደሚሰጥ ቅጠሉም እንደማይግፍ ዛፍ ናቸው፡፡ የሚሠሩት ሁሉ ይከናወንላቸዋል፡፡ 4 ክፉ ሰዎች ግን እንደዚህ አይደሉም፣ ክፉ ሰዎች ከዛፍ እንደሚራገፉና ነፋስም ጠርጎ እንደሚወስዳቸው እንደማይጠቅሙ ገለባዎች ናቸው፡፡ 5 ስለዚህ፣ እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ በሚፈርድበት ጊዜ፣ ክፉዎችን ይኮንናቸዋል፡፡ ከዚህም ሁሉ በላይ፣ ያሕዌ ዱሳንን በአንድ ላይ በሚሰበስብበት ጊዜ፣ ክፉዎች በዚያ ሊገኙ አይችሉም፡፡ 6 ያሕዌ ቅዱሳንን ይመራቸዋል ይጠንቃቸዋልም፤ ክፉዎች የሚሄዱበት መንገድ ግን እግዚአበሔር እነርሱን ለዘላለም ወደሚየጠፋበት አቅጣጫ ይወስዳቸዋል፡፡